Ankuar

Politics, culture and society in Ethiopia

አንኳሮች

COVID-19FEATUREDአንኳሮች

‎እጅ ከመታጠብ ባሻገር. . . (ሀገራችን ደሃ ነች፤ የታመመውን ሁሉ ተቀብሎ የሚያስታምም መንግሥትም ሆነ የጤና ባለሙያ የላትም)

ስለዚህ በቤትህ ውስጥ አንተ ወይም ከቤተሰብህ አንዱ ኳራንቲን መደረግ እንዳለባቸው ስታውቅ ማንኛውንም ንክኪ ማስወገድ እንዳለብህ፣ እንዲሁም እንዴት የሚለውን አስብበት፤ ለምሳሌ የታመመውን ሰው የቤት ውስጥ እንቅስቃሴ መገደብ፣ መፀዳጃ ቤት ያው የጋራ ስለሆነ ያ ሰው ገብቶ ከመቀመጥ በቀር ምንም እቃ እንዳይነካ ማድረግ፣ ድንገት የበር እጀታም ሆነ ሌላ ነገር ቢነካ ጓንት እንዳይለየው ከወዲሁ ማዘጋጀት፣ ንክኪ ሊኖራቸው የሚችሉ ማንኛውንም ቁሳቁሶች በአልኮል ወይም በተመሳሳይ ዘዴ ወዲያው ወዲያው ማፅዳት፣ የመተንፈሻ ጭንብል (ማስክ) እንዲጠቀም ማድረግ

Read More
COVID-19FEATUREDአንኳሮች

እድሉ ያመለጠን ይመስለኛል፤ ግን ሰውነታችንንም እንዳይነጥቀን እንዘጋጅ!

አንዴ ፈጣሪ አምጥቶታል፤ ብቻ ሰብዓዊነታችንን እንዳይነጥቀን! እንዳንዘራረፍ፣ እንዳንገዳደል፣ እንዳንበላላ! ለራሳችን የምናስበውን ያክል ለሌሎችም እናስብ፡፡ አደራ ሰውነታችንን እንዳንረሳ፣ አደራ!

Read More
NewsPoliticsአንኳሮች

«ከነጋዴ እና ከምሁር» የሚል የአራተኛ ክፍል ክርክር ላይ የለሁበትም!

እናም በቀደም ጠቅላይ ሚኒስትራችን አብይ አህመድ ምሁርነትን አረከሰ እየተባለ ከፍተኛ ውርጅብኝ እየወረደበት ነው፡፡ ይህ ሰው በሌሎች መድረኮች ላይ ስለእውቀት አስፈላጊነት ሳይናገር ቀርቶ አይመስለኝም፡፡ ኧረ እንዲያውም ስለ ‘አርቲፊሻል ኢንተሊጀንስ’ ምናምን የሆነ ውስዋስ ወስጥ ሁሉ ከቶን ነበር፡፡

Read More
COVID-19FEATUREDHealthአንኳሮች

የወዳጅ ምክር ስለኮሮና ቫይረስ

– ስንገናኝ ባልጨብጥህ፣ – ምን ያህል ብትናፍቀኝ ባልጠመጠምብህ፣ – ስታወራኝ ሁለት ክንድ ሆኜ ባዳምጥህ፣ – ምሳ እንደባህላች ገባታህ ላይ ባልቀርብ፣ – ከፍቅራችን የተነሳ ልታጎርሰኝ ስትሞክር እምቢኝ ብል፣ – ልታገኘኝ ፈልገህ አይመቸኝም ብልህ፣ – ቤትህ ደስታህን እንድካፈል ብትጋብዘኝና ብቀር፣ – እርምህን ብበላ፣– በእመቤቴ ይዤሃለሁ፣ አትቀየመኝ! እኔም ያንኑ ባይብህ አልቀየምህም!

Read More
FEATUREDአንኳሮች

ጀዋር የራሱ ጉዳይ፣ ሕጉን ግን በአግባቡ እንተርጉመው!

እናም ይህ የተለየ ሥርዓት አንቀፅ 22 (1) ላይ ይገኛል፡፡ አስቀድሞ ኢትዮጵያዊ የነበረና በሕግ የሌላ አገር ዜግነት ያገኘ ሰው፣ አንደኛ ኢትዮጵያ ተመልሶ መኖሪያውን እዚህ ካደረገ፣ ሁለተኛ ይዞት የነበረውን የሌላ አገር ዜግነት ከተወ፣ ሦስተኛ ዜግነት እንዲመለስለት ለኢሚግሬሽን (ለባለሥልጣኑ) ካመለከተ ኢትዮጵያዊ ዜግነቱን መልሶ ያገኛል ይላል፡፡ በቃ ሌላ ርቀት አይጠበቅበትም፤ ቅድመ-መርሆ (presumption) ተወስዷል በሕጉ፤ የአመልካቹ የማስረዳት ግዴታው (burden of proof) ተላልፏል ለባለሥልጣኑ፡፡ እነዚህ ሦስት ነገሮች ከተሟሉ ባለሥልጣኑ «ከዚህ በኋላ ዜጋ ሆነሃል» የማለት ሥልጣንም፣ ኃላፊነትም፣ ግዴታም የለበትም፡፡ ሆኗላ!

Read More
FEATUREDአንኳሮች

አንተ እየሸናህ ስትናፈስ፣ ትውልድ በልመና አፉን ሲፈታ

አማርኛን ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ ቢማሩ በመላው ሀገሪቱ ተዟዙረው እንዲሰሩ ያስችላቸዋል እያልክ ስትተነትን፣ ሕፃናቱ ግን ቀድመው ለምደውትና የትም መዟዟር ሳያስፈልጋቸው እዚሁ ቀዬያቸው ላይ የገቢ ምንጭ አድርገውታል – አማርኛን እየተኮላተፉም ቢሆን ይለምኑበታል፡፡

Read More