Ankuar

Politics, culture and society in Ethiopia

FEATURED

COVID-19FEATURED

የሀገር ውስጥ ስርጭት 55%፤ ንክኪያቸው የማይታወቅ 23% ደርሷል

የዛሬውን ውጤት ይበልጥ አሳሳቢ የሚያደርገው 45 ሰዎች የጉዞ ታሪክም ሆነ የታወቀ ንክኪ የሌላቸው መሆኑ ነው። ከነዚህም ውስጥ 43ቱ በአዲስ አበባ የተያዙ ናቸው። በአዲስ አበባ ሌሎች በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ ያላቸው 5 ሰዎችም መያዛቸው ተነግሯል።

Read More
COVID-19FEATURED

የሰሞኑ የኮቪድ-19 ቁጥሮች ምን ትርጉም አላቸው?

በዛሬው ውጤት ላይም ተጨማሪ ጥያቄ የሚያጭር ነገር አለ። የጉዞ ታሪክ አላቸው የተባሉት 5 ሰዎች አፋር እና ትግራይ ለይቶ ማቆያ እንደሚገኙ ተገልጿል። ነገር ግን በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ አላቸው ከተባሉት 6 ሰዎች ውስጥ አንድ ግለሰብ ኦሮሚያ ክልል አዳማ “ለይቶ መከታተያ” እንደሚገኝ ተገልጿል። “ለይቶ መከታተያ” የሚለው ሀረግ በመግለጫው የእንግሊዝኛ አቻ ላይ “Isolation” የሚለውን የሚወክል ሲሆን፣ ይህም በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ተለይተው ሕክምና የሚከታተሉበት ቦታ ነው። በለይቶ መከታተያ ተገኝቶ በቫይረሱ ሊያዝ የቻለበት ሁኔታ ተጋላጭነትን በአግባቡ ካለመቀነሰ የመጣ ከሆነ ለወደፊቱ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንደሚያሻ ያመላክታል።

Read More
FEATUREDፖለቲካ/ፍልስፍና

“ተከታታይነት ያለው የሥልጣን ሽግግር ሊኖር ይገባል” – ጀምስ ሐሪንግተን (1611-77)

ሐሪንግተን የጠቆማቸው አብዛኛዎቹ መርሆዎች የሊበራል መንግሥት መገለጫዎች መመዘኛ ለመሆን በቅተዋል፡- የተፃፈ ሕገ-መንግሥት፤ ምርጫና የመንግሥት ኃላፊዎች በአጭር ጊዜ የሥልጣን ዘመን መለዋወጥ፤ የሃይማኖት ነፃነት ዋስትናዎች፤ በመንግሥት ወጪ የሚሸፈን ለሁሉም የሚሰጥ ትምህርት።

Read More
COVID-19FEATURED

ኮቪድ-19 በስፋት እየተሰራጨ መሆኑን የዛሬው ውጤት ያረጋግጣል! (አሁንም አንዘናጋ!)

በየዕለቱ የሚሰጡ መረጃዎችን መሠረት በማድረግ፣ እስከዛሬ በሀገር ውስጥ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 77 ነው። ከእነዚህ ውስጥ፣ የዛሬዎቹን 19 ሰዎች ጨምሮ፣ 42 ሰዎች (55%) ንክኪያቸው እንዳልታወቀ የተገለፀ ነው። ይህም ከፍተኛ ስጋት ሲሆን፣ ከመቼውም በላይ ኅብረተሰቡ መዘናጋት እንደሌለበትና ጥንቃቄውን መጨመር እንዳለበት ይጠቁማል።

Read More
FEATUREDፖለቲካ/ፍልስፍና

“ሰዎች በመንግሥት ባይገደቡ ኖሮ ይሄን ጊዜ ተላልቀው ነበር” – ቶማስ ሆብስ (1588-1679)

በዚህ የተያያዘ አመክኒዮ አማካኝነት ማኅበረሰብ ይፈጠራል። የሚፈጠረውም በስምምነት ነው፤ ይህንንም ሆብስ ኮምፓክት (compact) ብሎ ይጠራዋል። . . . ሕይወቱ በመንግሥት አደጋ የተጋረጠባት ተገዥ – ለምን የሞት ፍርደኛ የሆነ ወንጀለኛ አይሆንም – ከተቻለው የመከላከል፣ አልያ ደግሞ የማምለጥ መብት አለው። በተመሳሳይ፣ በወራሪ ጠላት ሽንፈት የገጠመውን ገዥ፣ ተገዢዎች የማክበር ግዴታ የለባቸውም።

Read More
FEATUREDፖለቲካ/ፍልስፍና

“ንጉሡ ለሃይማኖት አባቶች መንፈሳዊ ምክር ተገዢ መሆን አለበት” – ቅዱስ ቶማስ አኩዊናስ (1225-74)

ነገሥታት ሊኖሩ የቻሉት ጥፋተኝነትን ከመግታትና እምነትን ከመፈተን ባሻገር እንዲሠሩ ነው፤ የመኖራቸው ምክንያት የጋራ መልካምን ወይም ሕዝባዊ ጥቅምን እንዲያረጋግጡ ነው፡፡ ስለዚህ ከዚህ በተቃራኒው ንጉሡ ለራሱ በግል ጥቅሙ ላይ ካተኮረ – ወይም በአርስቶትል “Politics” መጽሐፍ ክፍል ሦስት ላይ በቀረበው መልኩ ጨቋኝ (tyrant) ከሆነ – በእግዚአብሔር የተሾመበትን ዓላማ ክዷል፤ እናም ሕዝቦቹ ያከብሩት ዘንድ ምንም ግዴታ የለባቸውም፡፡

Read More
COVID-19FEATUREDNews

ኢትዮጵያ በአጠቃላይ 8698 የኮቪድ-19 የላብራቶሪ ምርመራዎችን አድርጋለች

እስካሁን የጉዞ ታሪክ ሳይኖራቸው፣ በተጨማሪም ቫይረሱ ከማን እንደተላለፈባቸው ያልታወቀ ሰዎች ቁጥር 15 ደርሷል። ይህ ቁጥር ጤና ሚኒስቴር በየዕለቱ ከሚሰጣቸው መግለጫዎች ላይ የተለቀመ ሲሆን፣ የንክኪያቸው ምንጭ ተጣርቶ የተረጋገጠበት ሁኔታ እስከዛሬ አልተገለፀም።

Read More
COVID-19FEATUREDNews

አካላዊ ርቀትን መጠበቅ ምን ያህል ጠቃሚ ነው?!

የታመመ ሰው የአየር ዝውውር በሌለበት ክፍል ውስጥ ለአምስት ደቂቃ በሚያወራበት ጊዜ፣ አንድ ሳል ከሚያመነጨው እኩል ብዙ ቫይረስ-አዘል ጠብታዎችን ሊያመነጭ ይችላል። “10 ሰዎች በዚያ ክፍል ቢኖሩ፣ እየጨመረ ይሄዳል”፣ ይላሉ ፓራቲም ቢስዋስ፣ በሴንት ሊውስ የዋሽንግተን ዩኒቨርሲቲ የኤሮሶልስ ባለሙያ።

Read More
COVID-19FEATUREDNews

ለይቶ የማቆየት አስገዳጅ እርምጃ ያስገኘው ፋይዳና የሀገር ውስጥ ስርጭት ሁኔታ

ሆኖም 24 ሰዎች አስገዳጅ ለይቶ የማቆየት እርምጃው ተግባራዊ ከተደረገ በኋላ ምንም ዓይነት የጉዞ ታሪክ ሳይኖራቸው እዚሁ ሀገር ውስጥ በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 11 የሚሆኑት ከነጭራሹ ከማን እንደያዛቸው ወይም ሊይዛቸው እንደቻለ አልታወቀም።

Read More
COVID-19FEATUREDNews

ኮቭድ-19 በኢትዮጵያ፤ የ30 ቀናት ቁጥሮች እና ገላፃዊ ትንታኔዎች

ሆኖም የአስገዳጅ ለይቶ ማቆያው እርምጃው ከተወሰደ በኋላና በዚህ አማካኝነትም በለይቶ ማቆያ ከነበሩ ሰዎች መካከል፣ ከውጭ ሀገር የመጡና በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 31 ነው። ይህም የእርምጃዎን ውጤታማነት በጉልህ ሊያሳይ የሚችል ነው።

Read More